Sport ስፖርት

Ethio-Berlin Sportklub

የኢትዮ በርሊን የእ ግር ኳስ ቡድን አመሰራረት

   የኢትዮ–በረሊን የዕግር ኳስ ቡድን በoctober 2014  ከ10  በማንበልጥ የመህበሩ አባላት  ወጣት መሳይ ሽማግሌዎች ( ወ.መ.ሽ ) እግር ለማፍታታት  ፣ ደም ለማዘዋወር ፣ በየአስሩ ደቂቃ እያረፍን በማህበራዊ ጉዳይ ላይ በመወያየት እንደዋዛ 

 በ schillerpark በየሳምንቱ እዑድ ቀጭን ልምምድ በማድረግ ተጀመረ።

በፎቶግራፍ ማስረጃነት እንደምናስተውለው ወቅቱ ብርዳማ ስለነበረ የዕጅ ጓንት ፣ ወፍራም ሹራብና ካፖርት ፣ የራስ ቅል ቆብና ኮፍያ በመድፋት ፣ የአዘቦት ልብስ  ለብሰን የስፖርት ጫማ በመጫማት ነበር መጫወት የጀመርነው ።

ውሎ አድሮ !  ጊዜው ብዙ ከኢትዮዽያና ኤርትራ በስደት ወደ ጀርመን የገቡበት ጊዜ ስለነበር የኛን የኳስ ልምምድ መውተርተር የሰሙ  ወጣቶች በብዛት ተቀላቀሉን ።

በዚህም ሂደት ቁጥራችን ከ4 ቡድን በለይ አሻቀበ መሄዱን በተረዱት ” ወ መ ሽ “ወች ምክክር  ጉዳዩ   ለኢትዮ– በርሊን መህበር ቀረበ። 

ከዚህ ቀጥሎ የስፖርት ክለቡን በተመለከት ከ አቶ ደረጀ መንገሻ የተዘጋጀ ዘገባ

ማህበሩን በሰፊው ከተወያየበት  በኋላ    

1— አዲስ የመጡትን ወገኖቻችን እዚህ ከቆየነው ጋር ለመቀራረብ  አንደሚረዳ:      

2– ልጆችንና ወጣቶችን በማገናኘት  በአካልና  መንፈስ ከማጎልበት ባሻገር የሃገራቸውን ባህል ቋንቋና ልማድ ለማስተዋወቅና ለማጠናከር  እንደሚያመች  አምኖበት: 

አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ገዝቶ ፣ አሰልጣኝ መድቦ 

የልጆችና የወጣቶች ቡድንአቋቁሞ:   

ኢትዮ— በርሊን የስፖርት ክለብ ብሎ ቡድኑን በመሰየም ስራውን ተያያዘው ።

በመቀጠልም በአውሮፓ ኢትዮጵያውያን ባህልና ስፖርት ፌደሬሽን ዓባልነት  ተመዝግበን በየዓመቱ በሚደረገው ውድድር ተሳታፊ ለመሆን በቃ ። 

በሂደቱም የኢየትዮ— በርሊን የእግር ኳስ ቡድን: 

2015 ፈረንክፈርት በተከናወነው  የኢትዮ– አውሮፓ ስፖርት ፌስቲቫል ኢትዮ—በርሊን  ቡድን ለመጀመርያ ጊዜ ተሳተፈ : 

በ2016 በሙኒክ  የኢትዮ–ጀርመን ካፕ  ተሳትፎ

የፀባይና ሦሥተኛ በመሆን የሁለት ዋንጫ ተሸላሚ በመሆን አጠናቋል  ።

በመቀጠልም በዚሁ ዓመት የልጆች የወጣቶችና የዋና ቡድኑን በመማሰለፍ ሦሥት ቡድን ይዞ ዴንሀግ / ሆላንድ ላይ በተዘጃው በአውሮፓ ኢትዮጵያውያን ባህልና ስፖርት ፌደሬሽን ፌስቲቫል ላይ በሁለቱ ታዳጊ ቡድኖች ሁለተኛ በመሆን ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ተካፍሏል ።

ከላይ በተጠቀሱትም ክንውኖች የማህበሩ ዓባሎች፣ ኢትዮጵያን የበርሊን ነዋሪወችና  ወዳጆቻችን  ደስተኛነታቸውን በመግለፅ ዕርዳታና ትብብራቸውን እስካሁን አላቋረጡብንም ።ለዚህም ምስጋናችን የላቀ ነው ።

የኢትዮ–ጀርመን ባህልና ስፖርት ፌደሬሽን የበለጠ ተጠናክሮና ተደራጅቶ የ2017 ቱን ዓመታዊ ስፖርት ፌስቲቫል አዘጋጅነት ለኢትዮ—በርሊን በመስጠቱ Juni 3/4  ለሀመጀመሪያ ጊዜ የሁለት ቀን ዝግጅት በማድረግ በኢትዮጵያ ስፖርት ዓለም ታሪክ  ዙሪያ በጣም ታዋቂ የሆኑትን አቶ ፍቅሩ ኪዳኔን የክብር ዕንግዳ አድርጎ ተጋባዥ በማድገግ  ብዙ ህዝብ ያሰባሰበ እጅግ የደመቀ በዓል ተግባራዊ አድርጓል ። በዚሁ ዓመት በፌዴሬሽኑ ታሪክ እጅግ አወዛጋቢ በነበረው የ2017 የሮም የስፖርት ዝግጅት ከሌሎች በርካታ የፌዴሬሽኑ ዓባል ከሆኑ ክለቦች ጋር በመሆን በተቃውሞ የዝግጅቱ ተካፊይ ሳይሆን ቀርቷል ። 

በ 2018 በሽቱጋርት/ ጀርመን ከ July 31— August 4  በተደረገደውም የአውሮፓ ስፖርት ፌስቲቫል የልጆችና ዋና ቡድኑን በማሰለፍ እንደገና የልጆቹ ቡድን የሁለተኛ ዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን የዋና ቡድኑም የተመሰገነ ተሳትፎ በማድረግ ግሩም  ጨዋታ በማሳየት ተደናቂነትን አትርፏል ።

2019 ከ July 31— August 3.Zurich / Switzerland ላይ በተደረገው: በአውሮፓ ኢትዮጵያውያን ባህልና ስፖርት ፌደሬሽን ፌስቲቫል ላይ እንደተለመደው ሙሉ ቡድኑን በማሰለፍና ቤተሰብ ፣ ደጋፊወቹን ይዞ በመገኘት እጅግ የደመቀና የተሳካ ዝግጅት ላይ ተሳትፏል ። በተለይ ከፌስቲቫሉ አዘጋጆች ፣ ከዙሪክ ኢትዮጵያን ነዋሪወችና የፌዴሬሽኑ ዓመራሮች ጋር እየተናበቡ በቅርብ በመስራት የኢትዮ-በርሊን ስፖርት ክለብ  መሪዎች “የኢትዮጵያ ቀን” በሚል መርሆ የዝግጅቱን ቦታ በኢትዮጵያ ባንዲራ እንዲሸበርቅና የተለያዩ የባህልና ሙዚቃ ትርኢቶች ተፈፃሚነት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል ።

2020 May 30/31 ሀምበርግ / ጀርመን ላይ ሊካሄድ የነበረው  በጀርመን የኢትዮጵያን ስፖርትና ባህል ፌስቲቫል

እንዲሁም:

ከ July 29— August 01

Amsterdam / Holland ላይ ሊደረግ ታስቦ የነበረው ዓመታዊ በአውሮፓ ኢትዮጵያውያን ባህልና ስፖርት ፌደሬሽን ፌስቲቫል ሁላችንም በምናውቀው የ Covid 19 ዓለማዊ ወረርሽኝ ምክንያት ዝግጅቱ ተፈፃሚነት ሳያገኝ ቀርቷል  ።